አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ከታወጀ (ከመስከረም 28 2ዐዐ9 ዓ.ም) ጀምሮ በዜጎች ላይ የሚፈፀም የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት በአስቸኳይ ይቁም!

አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ከታወጀ (ከመስከረም 28 2ዐዐ9 ዓ.ም) ጀምሮ

በዜጎች ላይ የሚፈፀም የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት በአስቸኳይ ይቁም!

የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ሰመጉ) የአስቸኳይ ግዜ አዋጁ ከታወጀበት ቀን ጀምሮ በዜጐች ላይ የተፈፀሙትን የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ይፋ አደረገ። ሰመጉ ሰኞ ግንቦት 21 ቀን 2009 ዓ。ም ባወጣው በ142ኛ ልዩ መግለጫው በተለያዩ የሃገራችን ክፍሎች በተለይም በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል፣ እንዲሁም በአዲስ አበባ እና በዙሪያዋ ባሉ ከተሞች የተፈፀሙና ሰመጉ ምርመራ አከናውኖ በቂ መረጃ እና ማስረጃ ያሰባሰበባቸውን የተለያዩ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ይፋ አድርጓል።

በዚህ ልዩ ሪፖርት በዜጐች ላይ የተፈፀሙ ህገወጥ ግድያዎች፣ ማቁሰል፣ድብደባ፣ ማሰቃየት፣ የጅምላ እስር እና ሌሎች የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ተካተዋል። ይህ የ142ኛው ልዩ ሪፖርት በተጠቀሱት ክልሎች በሚገኙ በ18 ዞኖች፣ በ42 ወረዳዎች እና ክፍለ ከተሞች የተፈፀሙትን የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች ብቻ የሚያካትት ነው። በልዩ ሪፖርቱ ማጠቃለያም ሰመጉ መንግስት ተገቢውን እውቅና፣ የመሥራት ነፃነት፣ ድጋፍና ጥበቃ እንዲያደርግለት ጠይቋል።

ሙሉውን ሪፖርት ለማግኘት ከዚህ በታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ

የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ 142ኛ ልዩ መግለጫ ግንቦት 2009 ዓ。ም

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

*

*

*