ሰመጉ 26ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ ሊያካሂድ ነው

የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ሰመጉ) 26መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔውን ያካሂዳል፡፡ ጠቅላላ ጉባዔው የፊታችን እሑድ መጋቢት 24 ቀን 2009 ዓ.ም. በሠራተኞች ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) አዳራሽ ከጠዋቱ 2፡30 ይጀመራል፡፡ በጉባዔው የ2008 – 2009 ዓ.ም. ዓመታዊ ሪፖርት፤ የውስጥ እና የውጭ ሪፖርት የሚቀርብ ሲሆን፣ የ2009 – 2010 ዓ.ም ዕቅድና በጀት ሪፖርትም ይቀርባል፡፡

በጉባዔው ላይ ከሰመጉ ስድስት የቀጠና ጽ/ቤቶች የተውጣጡ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴዎች አባላት ተካፋይ ይሆናሉ፡፡

ዓመታዊ የአባልነት ክፍያቸውን የከፈሉ አባላት መካፈል ይችላሉ፡፡ የአባልነት ክፍያ ያላሟሉ የሰመጉ አባላት በጉባዔው ዕለት ክፍያቸውን በመፈጸም ተካፋይ እንዲሆኑ ሰመጉ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡

 

የስብሰባ ቦታ –  በሠራተኞች ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) አዳራሽ – ቦሌ ፍላሚንጎ

የስብሰባ ቀን – መጋቢት 24/2009 ዓ.ም. ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

*

*

*