144ኛ ልዩ መግለጫ – በኢትዮጵያ ሶማሌ እና በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ ዞኖች የተፈፀሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች።

በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስትና በሶማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ውስጥ በሚገኙ የተለያዩ አካባቢዎች የተፈጸሙ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶችን በተመለከተ ሰብአዊ መብትች ጉባኤ ልዩ መግለጫውን ይፋ አድርጓል። በሰብአዊ መብቶች ጉባኤ 144ኛ ልዩ መግለጫ የሰብዓዊ መብቶ ጥሰቶ የተፈጸሙት ከጥር 2009 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ጥር 2010 ዓ.ም ባሉት 12ወራት ሲሆን ሪፖርቱ በዜጎች ላይ የተፈፀመ ግድያን፣ አስገድዶ መድፈርን እና መጠኑ የሰፋ የዜጎች መፈናቀልን አካቷል።

ይህ ሪፖርት ሁለት ክፍል ያለው ሲሆን በመጀመያው ክፍል የሶማሊ ክልል ልዩ ሀይል እና የመከላከያ ሰራዊት የፈፀሙት ጥቃት አንደሆነ ሪፖርቱ አካቷል። በምእራብ ሀረርጌ ዞን እና በባሌ ዞን ከሶማሊ ክልል ጋር በሚገኙ አዋሳኝ ቦታዎች የሶማሊ ክልል ሌዩ ሀይልና መከላከያ ሰራዊት በፈፀመው ጥቃት በምእራብ ሃረርጌ ዞን 160 ዜጎች ሲገደሉ በባሌ ዞን 96 ዜጎች ተገድለዋል፤ ይህኛው የሪፖርቱ ክፍል ጉዳት የደረሰባቸውንና የሟቾችን ስም ዝርዝር ይዞ የወጣ ሲሆን አስገድዶ መድፈርን እና የዜጎች መፈናቀልን አካቷል።

የልዩ መግለጫው ሁለተኛ ክፍል በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ውስጥ በሚገኙ የተለያዩ ዞኖችና ወረዳዎች ውስጥ በተነሱ ግጭትና ጥቃቶች ምክንያት ህይወታቸውን ያጡ የሶማሌ ብሔረሰብ ተወላጆችን ስም ዝርዝር ያካተተ ሲሆን ከኢትዮጵያ ሶማሌ ክልላዊ መንግስት ፖሊስ ኮሚሽን በተገኘ ሪፖርትና የሰመጉ ባለሙያዎች ቦታው ድረስ በመሄድ ከተጎጂዎች፣ ከተጎጂ ቤተሰቦችና  ከአይን እማኞች ባጣሩት መሰረት ሪፖርቱ በሸፈናቸው 12 ወራት ውስጥ በተፈፀመ ጥቃት 451 ዜጎች ህይወታቸውን አጥተዋል፤ ቁጥሩ የበዛ የዜጎች መፈናቀል፤ መደፈር እና የአካል ጉዳት በዚሁ ክፍል ተካቷል።

የሰመጉ 144ኛ ልዩ መግለጫ ሙሉውን ሪፖርት እዚህ ያገኛሉ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

*

*

*