በግብር ጭማሪው ላይ ቅሬታና ተቃውሞ ለሚያሰሙ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት የሚሰጠው መንግሥታዊ ምላሽና የጉዳዩ አያያዝ ሰብዓዊና የዜግነት መብቶቻቸውን የጠበቀ ሊሆን ይገባል፤ በክልሎች መካከል ለግጭት መንስኤ የሚሆኑ ጉዳዮችም በአስቸኳይ እልባት ይሰጣቸው

 

የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ በግብር ጭማሪው ላይ ከንግዱ ማህበረሠብ ለተነሳው ቅሬታና ተቃውሞ እንዲሁም በክልሎች መካከል ለሚነሱት ግጭቶች ምላሽ እንዲሰጣቸው ጠየቀ። ሰመጉ ጳጉሜ 04 ቀን 2009 ዓም ይፋ ባደረገው ጋዜጣዊ መግለጫ የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ‹‹አማካይ የቀን ገቢ ግምት›› በማለት በንግድ ማህበረሰቡ ላይ የጣለውን የግብር መጠን ተከትሎ ከንግድ ማህበረሰቡ የገቢ ግምትና የግብር አወሳሰኑ የቀን ገቢያችንን ያገናዘበ አይደለም፣ እጅግ የተጋነነ ነው በማለት ከፍተኛ ቅሬታ በአዲስ አበባ ከተማና በተለያዩ የሀገሪቱ ከተሞችና አካባቢዎች ያቀረበው ተቃውሞና አቤቱታ አሁንም እንደቀጠለ ሲሆን፤ ችግሩን ለመፍታት የመንግስት አካላት በንግዱ ማህበረሰብ ላይ የሚፈፅሙት ዛቻ፣ ማስፈራራት፣ የሱቅ ማሸግ፣ የተሽከርካሪ ሠሌዳ መፍታት እና ሕገ ወጥ እስር ሕገመንግስቱን የሚፃረር መሆኑን ሰመጉ ገልጿል።

በመግለጫው ሁለተኛ ክፍልም በሃገራችን የተለያዩ አካባቢዎች ከማንነት፣ ከአስተዳደርና ከድንበር ይገባኛል ጥያቄ ጋር በተያያዘ ግጭት እየተቀሰቀሰ እንደሆነ፤ በአንዳንድ አካባቢዎችም ውሎ አድሮ ሊቀሰቀስ እንደሚችል ስጋቱ የገለፀ ሲሆን፤ መንግስት ከሕብረተሰቡ ጋር በመመካከር አስቸኳይና ዘላቂ መፍትሔ እንዲሰጥ ሰመጉ ጥሪውን አቅርቧል።

ሙሉ መግለጫውን እዚህ ያግኙ HRCO Press Release September 09, 2017

 

 

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

*

*

*