ሰመጉ 26ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔውን አካሄደ

ሰመጉ 26መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔውን ትናንት መጋቢት 24 ቀን 2009 ዓ.ም. አካሄደ፡፡ ጉባዔው በሰመጉ ዋና ዳይሬክተር አቶ ብጽዓተ ተረፈ ‹‹የእንኳን ደህና መጣችሁ›› መልዕክት የተከፈተ ሲሆን፣ የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ የድርጅቱ መሥራችና አንጋፋ አባላት የምስጋናና የዕውቅና የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል፡፡

በተያያዘም፣ ዋና ዳይሬክተሩ ለሰመጉ መሥራች አባት ፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማሪያም ከድርጅቱ ምሥረታ ጀምሮ ላበረከቱት የላቀ አስተዋጽኦ እና ለሰመጉ የሀዋሳ ቤተ መጻሕፍት ላበረከቱት የመጻሕፍት ልገሣ በጉባዔው ስም ምስጋና ያቀረቡ አቅርበዋል፡፡ ፕሮፌሰር መስፍንም “ይህንን ያደረግሁት ለሽልማት ወይም ለዕውቅና ብዬ ሳይሆን ለሐገርና ለወገን ማድረግ ያለብኝን ግዴታ ለመወጣት በማሰብ ነው” ብለዋል፡፡

በዚህ 26ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ ላይ ከስድስቱም የሰመጉ የቀጠና ፅ/ቤቶች የተወከሉ የስራ አሰፈጻሚ ኮሚቴ አባላት፣ እንዲሁም አንጋፋና ወጣት አባላት ተገኝተውል፡፡ በተጓደሉ የሥራ አሰፈጻሚ ኮሚቴ አባላት ምትክ ምርጫ የተካሄደ ሲሆን የድርጅቱን ውስጣዊ አሠራሮች የሚቆጣጠር የውስጥ ኦዲተርም ተመርጧል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

*

*

*