Latest Posts

ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶችን ለማስከበር ሕዝብ ተስፋ የጣለበት አጋጣሚ እንዳይባክን!

ሰኔ 22 ቀን 2010 ዓ.ም – ከሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ሰመጉ) በወቅታዊ ጉዳይ ላይ የተሰጠ መግለጫ። መሉ መግለጫውን እዚህ  (ፒዲኤፍ) በመጫን ማውረድ የችላሉ።

 

 

መንግስት ለሰላም፣ ለሰብዓዊ መብቶች መከበርና ለዲሞክራሲ መስፈን ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳይ!!

መንግስት ለሰላም፣ ለሰብዓዊ መብት መከበር እና ለዲሞክራሲ መስፈን ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር እንዲያሳይ ሰመጉ ጠየቀ። የኢህአዴግ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ባካሔደው ስብሰባ የፖለቲካ ምሕዳሩ መጥበቡን፣ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች በየቦታው እንደሚታዩ እና ዲሞክራሲያዊ ባህል እንዲዳብር መንግስት ተገቢውን ጥረት አለማድረጉን በመገምገም የገዢው ፓርቲ አመራር ኃላፊነቱን እንደሚወስድ በመግለፅ ፓርቲው መግለጫ ማውጣቱ ይታወቃል።   የግንባሩ አባል ድርጅቶችም ታህሳስ 25 ቀን 2010 ዓም  በሰጡት መግለጫ ይህንን በድጋሚ ማረጋገጣቸው ይታወሳል።

ሰመጉ ታህሳስ 27 ቀን 2010 ዓም ባወጣው ጋዜጣዊ መግለጫ መንግስት ለመውሰድ ቃል የገባቸው እርምጃዎች በመልካም ጐኑ የተመለከተ ሲሆን በዘላቂነት ሰብዓዊ መብቶችን ለማስከበር፣ ዲሞክራሲያዊ ስርዓትን በሃገሪቱ ለመገንባትና የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት የህግ፣ የተቋማትና የአሰራር ማሻሻዮችን ማድረግ እንዳለበት ሰመጉ አሳስቧል።

ሙሉ መግለጫውን እዚህ ያግኙ  HRCO PR Jan 5 2018

በኢትዮጵያ ለብሔረሰብ ተኮር ጥቃቶችና ግጭቶች የማያዳግም የፖሊሲና የአፈጻጸም መፍትሄ ይሰጥ!

በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልላዊ መንግስት በጌዴኦ ዞን በተለያዩ ወረዳዎች እና በሐረሪ ክልላዊ መንግስት በሐረር ከተማ ውስጥ እየተፈፀሙ ያሉ የተለያዩ የመብት ጥሰቶች በአስቸኳይ ይቁሙ!

የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ(ሰመጉ) መንግስት ለብሔረሰብ ተኮር ጥቃቶች የማያዳግም የፖሊሲና የአፈፃፀም መፍትሔ እንዲሰጥ ጠየቀ። ሰመጉ በ143ኛ ልዩ መግለጫው በኢትዮጵያ ብሔርን መሠረት ያደረጉ ጥቃቶች እና ግጭቶች እጅጉን ተባብሰው መቀጠላቸውንና አሳሳቢ ቀውስና መዘዝ በማስከተል ላይ መሆናቸውን ገልጿል። መግለጫው በጌዴኦ ዞን በተለያዩ ወረዳዎች የብሔረሰቡ ተወላጅ ባልሆኑ ዜጐች ላይ የተፈጸመውን ግድያ፣ ድብደባ፣ የመኖሪያና የንግድ ቤቶች ቃጠሎ በዝርዝር አካቷል። በተጨማሪም በሐረሪ ክልል የአፍረንቀሎ የኦሮሞ ባህልና ታሪክ ማዕከልን ለመገንባት የመሠረት ድንጋይ መጣልን ተከትሎ በኦሮሞ ማሕበረሰብ ወጣቶች ላይ የደረሰውን የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶችንም ይፋ አድርጓል።

መንግስት ከብሔር ጋር ለተያያዙ ጥቃቶች እና ግጭቶች በቂ ትኩረት ባለመስጠቱ የበርካታ ዜጐች ህይወት መጥፋቱን፣ አካል መጉደሉን፣ በመቶ ሺዎች ቤት ንብረታቸውን ጥለው እንዲሰደዱ መገደዳቸውን አስታውሶ፤ ከፌዴራል እስከ ክልል ያሉ የመንግስት ባለሥልጣናት ራሳቸውን እንዲመለከቱ እና ህዝብን ከህዝብ ከሚያጋጭና ሐገርን ከሚጐዳ ድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ሰመጉ ጠይቋል። መንግሥትም ለጉዳዩ በቂ ትኩረት ሰጥቶ ዘለቄታዊ መፍትሔ እንዲፈልግለት አሳስቧል፡

ሙሉ መግለጫውን እዚህ ያግኙ

በግብር ጭማሪው ላይ ቅሬታና ተቃውሞ ለሚያሰሙ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት የሚሰጠው መንግሥታዊ ምላሽና የጉዳዩ አያያዝ ሰብዓዊና የዜግነት መብቶቻቸውን የጠበቀ ሊሆን ይገባል፤ በክልሎች መካከል ለግጭት መንስኤ የሚሆኑ ጉዳዮችም በአስቸኳይ እልባት ይሰጣቸው

 

የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ በግብር ጭማሪው ላይ ከንግዱ ማህበረሠብ ለተነሳው ቅሬታና ተቃውሞ እንዲሁም በክልሎች መካከል ለሚነሱት ግጭቶች ምላሽ እንዲሰጣቸው ጠየቀ። ሰመጉ ጳጉሜ 04 ቀን 2009 ዓም ይፋ ባደረገው ጋዜጣዊ መግለጫ የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ‹‹አማካይ የቀን ገቢ ግምት›› በማለት በንግድ ማህበረሰቡ ላይ የጣለውን የግብር መጠን ተከትሎ ከንግድ ማህበረሰቡ የገቢ ግምትና የግብር አወሳሰኑ የቀን ገቢያችንን ያገናዘበ አይደለም፣ እጅግ የተጋነነ ነው በማለት ከፍተኛ ቅሬታ በአዲስ አበባ ከተማና በተለያዩ የሀገሪቱ ከተሞችና አካባቢዎች ያቀረበው ተቃውሞና አቤቱታ አሁንም እንደቀጠለ ሲሆን፤ ችግሩን ለመፍታት የመንግስት አካላት በንግዱ ማህበረሰብ ላይ የሚፈፅሙት ዛቻ፣ ማስፈራራት፣ የሱቅ ማሸግ፣ የተሽከርካሪ ሠሌዳ መፍታት እና ሕገ ወጥ እስር ሕገመንግስቱን የሚፃረር መሆኑን ሰመጉ ገልጿል።

በመግለጫው ሁለተኛ ክፍልም በሃገራችን የተለያዩ አካባቢዎች ከማንነት፣ ከአስተዳደርና ከድንበር ይገባኛል ጥያቄ ጋር በተያያዘ ግጭት እየተቀሰቀሰ እንደሆነ፤ በአንዳንድ አካባቢዎችም ውሎ አድሮ ሊቀሰቀስ እንደሚችል ስጋቱ የገለፀ ሲሆን፤ መንግስት ከሕብረተሰቡ ጋር በመመካከር አስቸኳይና ዘላቂ መፍትሔ እንዲሰጥ ሰመጉ ጥሪውን አቅርቧል።

ሙሉ መግለጫውን እዚህ ያግኙ HRCO Press Release September 09, 2017

 

 

HRCO releases the Executive Summary of the 142nd Special Report

HRCO 142nd Special Report English Executive summary

In anticipation of the translation of the 142nd Special Report from Amharic to English, HRCO releases the Executive Summary of the report. The Special Report shows the findings of the investigations regarding human rights violations committed after the issuance of the State of Emergency Declaration. In the report, HRCO calls on the Government to stop commission of human rights violations, to redress victims of violations and take measures to prevent further violations.

See Here.