145ኛ ልዩ መግለጫ – በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን በወልዲያ እና አካባቢው የተፈፀመ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት – ነሐሴ 03 ቀን 2010 ዓ.ም

የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ በ145ኛ ልዩ መግለጫ የተመለከተው በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በሰሜን ወሎ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች ውስጥ የተፈጸሙትን የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶችን ሲሆን የመብት ጥሰቱ የተፈጸመው ከሕዳር 24 ቀን 2010 .ም ጀምሮ እስከ የካቲት 04 ቀን 2010 .ም ድረስ ነው።  ሰመጉ ባለሙያዎቹን ወደ አካባቢው ልኮ የማጣራት ሥራውን የሰራው ከየካቲት 05 እስከ የካቲት 12 ቀን 2010 .. ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ ነው፡፡ በዚህም መሰረት በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ወልደያ ከተማ፣ ወልደያ ዙሪያ ወረዳ፣ ቆቦ፣ ሮቢት፣ መርሳ፣ ውርጌሳ እንዲሆም በደቡብ ወሎ ደሴ የተፈጠሩት የሰብአዊ መብት ጥሰቶች መርምሮ በዚህ መግለጫ አካቷል። በዚህም መሰረት የሰው ህይት እንደጠፋ እና የአካል ጉዳት እንደደረሰ ሪፖርቱ በምስል አስደግፎ አቅርቧል። ሙሉ መግለጫውን በፒዲኤፍ እዚህ ያገኛሉ ።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

*

*

*