መንግስት ለሰላም፣ ለሰብዓዊ መብቶች መከበርና ለዲሞክራሲ መስፈን ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳይ!!

መንግስት ለሰላም፣ ለሰብዓዊ መብት መከበር እና ለዲሞክራሲ መስፈን ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር እንዲያሳይ ሰመጉ ጠየቀ። የኢህአዴግ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ባካሔደው ስብሰባ የፖለቲካ ምሕዳሩ መጥበቡን፣ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች በየቦታው እንደሚታዩ እና ዲሞክራሲያዊ ባህል እንዲዳብር መንግስት ተገቢውን ጥረት አለማድረጉን በመገምገም የገዢው ፓርቲ አመራር ኃላፊነቱን እንደሚወስድ በመግለፅ ፓርቲው መግለጫ ማውጣቱ ይታወቃል።   የግንባሩ አባል ድርጅቶችም ታህሳስ 25 ቀን 2010 ዓም  በሰጡት መግለጫ ይህንን በድጋሚ ማረጋገጣቸው ይታወሳል።

ሰመጉ ታህሳስ 27 ቀን 2010 ዓም ባወጣው ጋዜጣዊ መግለጫ መንግስት ለመውሰድ ቃል የገባቸው እርምጃዎች በመልካም ጐኑ የተመለከተ ሲሆን በዘላቂነት ሰብዓዊ መብቶችን ለማስከበር፣ ዲሞክራሲያዊ ስርዓትን በሃገሪቱ ለመገንባትና የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት የህግ፣ የተቋማትና የአሰራር ማሻሻዮችን ማድረግ እንዳለበት ሰመጉ አሳስቧል።

ሙሉ መግለጫውን እዚህ ያግኙ  HRCO PR Jan 5 2018

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

*

*

*