ሂውማን ራይትስ ዎች ሰኔ 9 ቀን 008 ዓ ም ባወጣው ባለ 61 ገጽ ሪፖርት ” `ጭካኔ የተሞላበት አፈና`_የግድያ እና የእስራት ምላሽ፤ ለኢትዮጵያ የኦሮሞ ተቃውሞ” የኢትዮጵያ መንግሥት ተቃውሞውን ለመቆጣጠር በወሰደው ከመጠን ያለፈ የሃይል ርምጃ ከ400 በላይ የሚሆኑ ዜጐች መገደላቸውን፣ ከአስር ሺህ በላይ መታሰራቸውን፣ ሌሎች የመብት ጥሰቶችም መፈጸማቸውን ገልጿል።

Just another WordPress site
Just another WordPress site
ሂውማን ራይትስ ዎች ሰኔ 9 ቀን 008 ዓ ም ባወጣው ባለ 61 ገጽ ሪፖርት ” `ጭካኔ የተሞላበት አፈና`_የግድያ እና የእስራት ምላሽ፤ ለኢትዮጵያ የኦሮሞ ተቃውሞ” የኢትዮጵያ መንግሥት ተቃውሞውን ለመቆጣጠር በወሰደው ከመጠን ያለፈ የሃይል ርምጃ ከ400 በላይ የሚሆኑ ዜጐች መገደላቸውን፣ ከአስር ሺህ በላይ መታሰራቸውን፣ ሌሎች የመብት ጥሰቶችም መፈጸማቸውን ገልጿል።

ሰመጉ 141ኛ ልዩ መግለጫውን ይፋ አደረገ።
HRCO 141st Special Report Amharic Scanned
“በኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት መሠረት የማንነት ጥያቄ በሚያነሱ ዜጎች ላይ የሚፈጸም ግድያ፡ ሕገወጥ እስራት፡ አፍኖ መሠወር፡ ማፈናቀልና ንብረት መንጠቅ በአስቸኳይ ይቁም!” በሚል ባወጣው መግለጫ የወልቃይት፡ የቅማንት፡ የቁጫና የኮንቶማ ማህበረሰቦች አባላት ያነሷቸውን የማንነት ጥያቄዎች ተከትሎ በየክልሎቹ የተነሱ ግጭቶች የደረሰውን የሰው ህይወት መጥፋት፤ የአካል መጉደል፤ ህገወጥ እስራት፤ ድብደባ፤ የንብረት ውድመትና የተለያዩ ማህበራዊ ቀውሶችን አጋልጧል።
ሰመጉ 141ኛ ልዩ መግለጫውን ይፋ አደረገ።
HRCO 141st Special Report Amharic (Sene 01 2008)
“በኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት መሠረት የማንነት ጥያቄ በሚያነሱ ዜጎች ላይ የሚፈጸም ግድያ፤ ሕገወጥ እስራት፤ አፍኖ መሠወር፤ ማፈናቀልና ንብረት መንጠቅ በአስቸኳይ ይቁም!” በሚል ባወጣው መግለጫ የወልቃይት፤ የቅማንት፤ የቁጫና የኮንቶማ ማህበረሰቦች አባላት ያነሷቸውን የማንነት ጥያቄዎች ተከትሎ በየክልሎቹ የተነሱ ግጭቶች የደረሰውን የሰው ህይወት መጥፋት፤ የአካል መጉደል፤ ህገወጥ እስራት፤ ድብደባ፤ የንብረት ውድመትና የተለያዩ ማህበራዊ ቀውሶችን አጋልጧል።
የሪፖርቱን ሙሉ ዝርዝር ለማግኘት የሚከተለውን ሊንክ ይጫኑ
HRCO 141st Special Report Amharic (Sene 01 2008)
“በኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት መሠረት የማንነት ጥያቄ በሚያነሱ ዜጎች ላይ የሚፈጸም ግድያ፡ ሕገወጥ እስራት፡ አፍኖ መሠወር፡ ማፈናቀልና ንብረት መንጠቅ በአስቸኳይ ይቁም!!” በሚል ባወጣው 141ኛ ልዩ መግለጫ የወልቃይት፡ የቅማንት፡ የቁጫና የኮንቶማ ማህበረሰቦች አባላት ያነሷቸውን የማንነት ጥያቄዎች ተከትሎ በየክልሎቹ የተነሱ ግጭቶች የደረሰውን የሰው ህይወት መጥፋት፤ የአካል መጉደል፤ ህገወጥ እስራት፤ ድብደባ፤ የንብረት ውድመትና የተለያዩ ማህበራዊ ቀውሶችን አጋልጧል።
ሰመጉ ባደረገው ምርመራ የወልቃይት ተወላጆች ህወሃት በትጥቅ ትግል ላይ ከነበረበት ግዜ ጀምሮ በተለያዩ ቦታዎችና ግዜያት “እኛ አማሮች እንጂ ትግሬዎች አይደለንም” በማለት የአማራ ብሔረተኝነት የማንነት ጥያቄ ሲያነሱ መቆየታቸውን አስታውሶ፤ ተቃውሟቸውን በተከታታይ በሰላማዊ መንገድ ባሰሙ የወልቃይት ማሕበረሠብ አባላት ላይ በአካባቢው የሚገኙ የትግራይ ክልል መንግሥት የፀጥታ ሃይሎች መሆናቸውን አብራርቷል።
ሰመጉ የማንነት ጥያቄ በማንሳታቸው ብቻ ከወልቃይት አካባቢ በትግራይ ክልል መንግሥት የፀጥታ ሃይሎች የተገደሉ 34 ሰዎች፤ ታፍነው የደረሱበት ያልታወቀ 93 ሰዎች፤ ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉ 137 ሰዎችን ጨምሮ ድብደባና ማሠቃየት የደረሰባቸውን ሰዎች ስም ዝርዝር ማግኘት ችሏል። በተመሳሳይም የቅማንት ማሕበረሰብን የብሔረሰብን የማንነት ጥያቄ ተከትሎ የአማራ ክልል የጸጥታ ኃይሎች ጥቅምት 22 2008 ዓም በአርማጭሆ ወረዳ፤ ማውራ ቀበሌ ውስጥ በወሰዱት የኃይል እርምጃ በህገወጥ መንገድ የተገደሉ 22 ሰዎች ዝርዝር ለማጣራት ተችሏል።
“በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች ሕዝቦች ክልላዊ መንግሥት በጋሞጎፋ ዞን በአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ በላንቴ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ውስጥ በወላይታ እና በኦቾሎ ብሄረሰብ አባላት መካከል በ1992 ዓ.ም በይዞታ ይገባኛል ሰበብ በተፈጠረ ግጭት በወላይታ ተወላጆች ላይ የሕይወት መጥፋት ፣ የንብረት መወደም እና የወላይታ ብሄረሰብ ተወላጆች ከእድር እንደማስወጣት ያሉ የተለያዩ የማሕበራዊ ሕይወት ችግሮች ደርሰው ነበር።
ይህን ተከትሎ ከእድር እንዲወጡ የተደረጉት የወላይታ ብሄረሰብ ተወላጆች ከሌሎች ብሄረሰብ አባላት ጋር በመኾን አዲስ እድር በማቋቋም እየተረዳዱ የቆዩ ሲሆን ታህሳስ 3, 1999 ዓ.ም በላንቴ ቀበሌ ገበሬ ማሕበር ውስጥ በኦቾሎ ብሄረሰብ እድር ውጭ ሌላ እድር ሊኖር ስለማይገባ በአስቸኳይ እንድታፈርሱ የሚል ትእዛዝ ከላንቴ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ሊቀመንብር ከአቶ አለማየሁ አሻ እና ከኦቾሎ ባህል አስፈጻሚዎች ለእድሩ አመራር ኮሚቴዎች ትእዛዝ ማስተላለፉን እና ለማፍረስ ፈቃደኛ ባለመኾናቸው ምክን ያት በተለያዩ ጊዜያት የእድሩን መገልገያ እቃዎች ለመውሰድ ሙከራዎች መደረጋቸውን እና ይህንንም ህገ ወጥ ድርጊት በወቅቱ ከወረዳ እስከ ዞን አስተዳደር ድረስ ቢያሳውቁም መፍት ሄ ሊያገኙ አልቻሉም።”
ተጨማሪ እዚህ ያንብቡ